በቀናቶች ውስጥም ከጋቦን አየር ንብረት ጋር ተመሳሳይነት ባላቸው አዋሳ አሊያም አዳማ በመሄድ ልምምዱን እንደሚሰራ ተሰምቷል፡፡
ታዳጊ ብሄራዊ ቡድኑ አፍሪካ ዋንጫው ላይ መሳተፉን ለማረጋገጥ የፊታችን እሁድንም በጉጉት እየጠበቀ ይገኛል፡፡ ፊፋ በስፖርታዊ ጉዳዮች ላይ የመንግስት ጣልቃ ገብነትን ተመልከቶ ማሊ ላይ የጣለውን ቅጣት ተከትሎ የማሊ መንግስት እስከ ሚያዝያ 22 ምላሽ ሰጥቶ የቀድሞ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ሀላፊዎችን ወደ ቦታቸው ካልመለሰ ማሊን ለቀጣዮቹ 2 አመታት ከማንኛቸውም አለማቀፋዊ ውድድሮች ያግዳል፡፡
ይህንን ተከትሎም በ2017ቱ የአፍሪካ ዋንጫ በመጨረሻው ማጣሪያ በማሊ በድምር ውጤት ተሸንፋ ከውድድሩ ውጭ የነበረችው ኢትዮጵያም በውድድሩ ለመሳተፍ ይሄንን ቀን በናፍቆት ትጠብቃለች፡፡







No comments: