በሁለተኛው ዙር መጠነኛ መዳከም አሳይቶ የነበረው አዳማ ከነማም በአዲስ አባባ ስቴዲየም ባሳለፍነው ሳምንት ፋሲል ከነማን ከረታው አዲስ አበባ ከነማ ጋር ይጫወታል፡፡
ጅማ አባቡናን ባለቀ ሰአት በተቆጠረ ግብ በመርታት ዋንጫ ፉክክር ውስጥ ያለው ሲዳማ ቡና ከኤሌክትሪክ ጋር በ10›30 ሲጫወት ጅማ አባቡና ወላይ ዲቻን ጅማ ላይ ያስተናግዳል፡፡
አርባምንጭ ከነማ እና መከላከያ የሚያደርጉት ጨዋታም ሌላኛው ተጠባቂ የሊጉ 25ኛ ሳምንት ጨዋታ ነው፡፡ የፈታችን ረቡዕ ደግሞ ደደቢት ድሬዳዋ ከነማን ሲገጥም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደግሞ በ10›30 በርካታ ጨዋታዎችን በአዲስ አበባ ስቴዲየም መርታት ከቻለው ፋሲል ከነማ ይጫወታሉ፡፡
የዕለቱ ተጠባቂ እና ወሳኝ ጨዋታ ደግሞ በወልዲያ ሼህ መሀመድ አሊ አላሙዲን ስቴዲየም በወልዲያ ከነማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚደርግ ሲሆን ፈረሰኞቹ የፊታችን ረቡዕ በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ውድድር ላይ በምድብ ድልድል ከማን ጋር እንደሚገኛኙ ከማወቃቸው በፊት የሚያደርጉት ወሳኝ ጨዋታ ነው፡፡







No comments: